፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨
" ብሩህ አዕምሮዎች በክህሎት የበቁ ዜጎች" በሚል መሪ ቃል ሲካሄድ በቆየው 15ኛው የቴክኒክና ሙያ ሳምንት በከተማ ደረጃ በተካሔደው የዕውቅናና የማጠቃለያ መርሀ-ግብር ላይ በአጠቃላይ አፈፃፀም ከ 15ቱም ኮሌጆች 2ኛ በመውጣት ከአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ስራ እና ክህሎት ቢሮ የዋንጫ እና የምስጋና ምስክር ወረቀት ተበረክቶልናል። ስለሆነም ለውጤቱ መምጣት የላቀ አፈፃፀም የነበራቸው ዲፓርትመንቶች ፣ ዳይሬክቶሬቶች ፣ አስተዳደር ሰራተኞች ፣ አሰልጣኞች ፣ ሰልጣኞች እና ኢንተርፕራይዞች እንደየ አፈፃፀማቸው እውቅና እና ሽልማት በኮሌጁ ዲኖች ተበርክቶላቸዋል ። የአቃቂ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ዋና ዲን አቶ ፀጋዬ አዱኛ በበጀት ዓመቱ በረካታ ስኬቶች እንደመዝገቡ አስተዋፅኦ ላበረከቱ የኮሌጁ ማህበረሰብ እና ባለድርሻ አካላት ልባዊ ምስጋናቸውን አቅርበዋል ።
በጋራ እንችላለን !!!





.