ሁሉም ኢትዮጵያዊ ነገ ሀምሌ 24 ለተመሳሳይ አለማ በነቂስ ወጥቶ አሻራውን ያኖራል!
በነገው ዕለት ከማለዳው አስራ ሁለት ሰዓት ጀምሮ በአንድ ጀንበር 700 ሚሊዮን ችግኞችን ለመትከል ሁሉም ኢትዮጵያዊ ከያለበት በነቂስ ወጥቶ አረንጏዴ አሻራውን ያኖራል::
“በመትከል ማንሰራራት” የሚለውን መሪ ቃል አንግበን ህፃን አዋቂ ሳንል ሁላችንም ኢትዮጵያውያን እንደ ከዚህ ቀደሙ ሁሉ ተባብረን አሻራችንን እናኑር፡፡
አዲስ አበባ ከተማችንም በነገው እለት የችግኝ ተከላ መረሃ ግብር ቅድመ ዝግጅት አጠናቃለች::
.